ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ሽያጭ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ (በድጋሚ የወጣ) የጨረታ ቁጥር፡ ፀባ/06/2025-26

 

የተሸከርካሪዎቹ ዝርዝር መረጃ

ተ. ቁ

የሞዴሉ አይነት

ብዛት

የተመረተበት ዓ.ም

1

Hyundai Tucson

05

2021/Korea

 

ፀሐይ ባንክ አ.ማ ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የቀረበውን የጨረታ መመሪያ እና መመዘኛዎች የሚያሟላ ማንኛውም ፍላኀት ያለው ተጫራች መወዳደር ይችላል፡፡

  1. ተጫራቾች ለጨረታ የቀረቡትን ተሸከርካሪዎች በቅሎ ቤት አካባቢ በሚገኘው የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ከመጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ዘወትር በስራ ሰዓት ጠዋት ከ3፡00-5፡30 ከሰዓት ከ8፡00-10፡30 መመልከት ይችላሉ::
  2. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከመጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ) ፀሐይ ባንክ ዋናው መስሪያ ቤት ላይ በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000033657 ገቢ በማድረግ የጨረታውን ሰነድ ማግኘት ይችላሉ::
  3. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ለእያንያንዱ ተሸከርካሪዎች በተናጥል የመነሻ ዋጋውን 2% (ሁለት በመቶ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ) በፀሐይ ባንክ ስም በማዘጋጀት ማስያዝ ይኖርባቸዋል:: ተጫራቾች ከአንድ በላይ ተሸከርካሪ መጫረትና መግዛት ይችላሉ፡፡
  4. ጨረታው መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ከቀኑ 9፡15 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው እና ታዛቢዎች በተገኙበት በባንኩ ዋና መስሪያቤት 5ኛ ፎቅ በሚገኘው የፋሲሊቲ አስተዳደር መምሪያ የሚከፈት ይሆናል፡፡
  5. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በጨረታ ሰነዱ ላይ ባለዉ የዋጋ ማቅረቢያ በመሙላት ዋናዉንና ኮፒዉን በተለያዩ ፖስታ በማድረግና ሁለቱን ፖስታዎች በአንድ ላይ በሌላ ፖስታ ዉስጥ አድርገው በማሸግ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ::
  6. የጨረታው አሸናፊ ያሸነፉትን ተሸከርካሪ ሙሉ ክፍያ በመክፈልና የአሸናፊነት መግለጫ ደብዳቤ ከባንኩ ካገኙበት ጊዜ ጀምሮ በሚቆጠር በ10 ቀናት ውስጥ ለባንኩ ገቢ በማድረግ መኪናውን መረከብ ይኖርበታል:: በተጠቀሰው ቀናት ውስጥ ያልከፈለ ተጫራች ለጨረታው ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይደረጋል፡፡
  7. በጨረታው ተሳትፈው ላላሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲፒኦ ወዲያውኑ ተመላሽ ይደረግላቸዋል:
  8. የጨረታው አሸናፊ ለስም ማዛወሪያና ሌሎች ተጓዳኝ ወጪዎችን በሙሉ የሚሸፍን ይሆናል::
  9. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥሮች 0114705613/0114706033 ይደውሉ