"በዘላቂነት ለመማቋቋም ከሚመለከታቸው የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ጋር እየሠራን ነው፡፡" - የፀሐይ ባንክ ባቲ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ

 

የፀሐይ ባንክ ባቲ ቅርንጫፍ በር ላይ ሙዚቃ እየተጫወተ ተቀርጾ ተንቀሳቃሽ ምስሉ በቲክቶክ ገጽ ላይ ሲዘዋወር የነበረውን ከድር አብዱ የተባለ ግለሰብን ባንካችን በአካል አግኝቶታል፡፡

ፀሐይ ባንክ የከድርን የዕለት ችግር ለመቅረፍ ልብስ እንዲቀይር አድርጓል፡፡ ተጨማሪ ደግሞ በግለሰቡ እህት እና በልጁ ስም የባንክ ሒሳብ ተከፍቶላቸው ገንዘብ እንዲቀመጥለትም ተደርጓል፡፡

ከድር እና ቤተሰቡ ፀሐይ ባንክ ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው፤ በተደረገለት ድጋፍ በዘላቂነት ኑሮውን ለመለዋጥ እንደሚሠሩ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

የፀሐይ ባንክ ከአካባቢው የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ጋር በመሆን ግለሰቡን በዘላቂነት ለማቋቋም እየሠራ መሆኑን የፀሐይ ባንክ ባቲ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ ተስፋዬ አራጋው ገልፀዋል፡፡

ፀሐይ ባንክ
ለሁሉ!

#Tsehay_Bank #For_All